ለልጆች አካላዊ እና አዕምሮአዊ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው የተማሪዎች የወተት ምገባ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለፀ ።

‎ይህ የወተት ምገባው ፕሮግራም በወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር እና በወላይታ ልማት ማህበር SNV BRIDGE+ ፕሮጀክት ትብብር በከተማው ባሉ 8 የመንግስት ቅድመ መደበኛ ት/ቤቶች ላይ እየተተገበረ የሚገኝ ሲሆን አጠናክሮ ለማስቀጠል በማሰብ ከማህበሩ ማኔጅመንት አባላት እና ከተወጣጡ ከማህበሩ ሠራተኞች ጋር ውይይት ተደርጓል ። ‎በመድረኩ የተገኙት የወላይታ ልማት ማህበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሰፋ ናና በንግግራቸው ማህበሩ ይህን […]

ለልጆች አካላዊ እና አዕምሮአዊ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው የተማሪዎች የወተት ምገባ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለፀ ። Read More »

ወላይታ ልማት ማህበር የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማሳደግ የያዘውን ዕቅድ ዕውን ለማድረግ ከተለያዩ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ጋር እየሰራ ይገኛል ።

‎ማህበሩ በዛሬው ዕለትም ከዚህ ቀደም አብሮት ከሚሰራው ET-LEARNS ከተሰኘው ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመሆን ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 310 ክሮም ኮምፒውተር እና 10 ሰርቨሮችን ከነአክሰሰሪያቸው ለተለያዩ ት/ቤቶች አበርክቷል ። ‎‎በመድረኩ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የወላይታ ልማት ማህበር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ገብረመስቀል ጫላ የወላይታ ማህበረሰብ ያለውን

ወላይታ ልማት ማህበር የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማሳደግ የያዘውን ዕቅድ ዕውን ለማድረግ ከተለያዩ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ጋር እየሰራ ይገኛል ። Read More »

‎ማህበሩ በተፈጥሮ አደጋ የተጎዱ ዜጎችን መልሶ በማቋቋም ረገድ የድርሻዉን እያበረከተ ነዉ።

‎ወላይታ ልማት ማህበር ዜጎች የተሻለ ኑሮ እንዲኖሩ ለማስቻል በያዘዉ ዕቅድ የተለያዩ ድጋፎችን በማመቻቸት የድርሻዉን እየተወጣ መቆየቱ ይታወቃል። ‎ማህበሩ ባሳለፍነዉ ዓመት በካዎ ኮይሻ ወረዳ በመሬት መንሸራተት አደጋ የተጎዱ ዜጎችን በመደገፍና መልሶ በማቋቋም ሂደት ከመንግስትና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር በመሆን የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ የቆየ ሲሆን በዛሬዉ ዕለት በዞነነ አስተዳደርና በተለያዩ አካላት ድጋፍ የሰራቸዉን መኖሪያ ቤቶች በአደጋዉ ምክንያት

‎ማህበሩ በተፈጥሮ አደጋ የተጎዱ ዜጎችን መልሶ በማቋቋም ረገድ የድርሻዉን እያበረከተ ነዉ። Read More »

ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚተገበር የትምህርት ፕሮጀክት ማስጀመሪያ ተካሄደ፡፡

ወላይታ ልማት ማህበር በሰው ሀብት ልማት ዘርፍ ከአጋር ድግርጅቶች ጋር በመተባበር በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረገ እንደቆየ ይታወቃል፡፡ ማህበሩ ከነዚህ አጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ከመንግስት ጎን በመሆን የራሱን ድርሻ አበርክቷል፤ እያበረከተም ነው፡፡ ማህበሩ በዛሬው ዕለት በወላይታ ዞን አምስት መዋቅሮች የሚተገብረውን የዳግም ትምህርት ዕድል ፕሮጀክት አስጀምሯል፡፡ ፕሮጀክቱ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልልና ከወላይታ ዞን ከተለያዩ

ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚተገበር የትምህርት ፕሮጀክት ማስጀመሪያ ተካሄደ፡፡ Read More »

ልማት ማህበሩ ከሳቫና ፕሪንቲንግ ጋር በመተባበር ለአራት ትምህርት ቤቶች ከ1.1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አበረከተ።

ወላይታ ልማት ማህበር የልማት ስራዎችን ከተለያዩ አጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን ይሰራል። ማህበሩ በሰዉ ሀብት ልማት በአጋርነት ከሚሰራቸው ተቋማት አንዱ ሳቫና ፕሪንቲንግ ሲሆን ለዘንድሮ የትምህርት ዘመን በወላይታ ዞንና ወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ለሚገኙ አራት ትምህርት ቤቶች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል። ድጋፉ የደብተር፣ እስክሪብቶ እና ሞንቴሶሪ ዕቃዎችን ያካተተ እንዲሁም በገንዘብ ሲተመን ከ1.1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ነዉ።

ልማት ማህበሩ ከሳቫና ፕሪንቲንግ ጋር በመተባበር ለአራት ትምህርት ቤቶች ከ1.1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አበረከተ። Read More »

በመትከል ማንሰራራት

የማህበሩ ሰራተኞች በወላይታ ሶዶ ከተማ ከሚገኙ ተቋማት ጋር በመሆን የአረንጓዴ አሻራ አኖሩ፡፡ ወላይታ ልማት ማህበር በአገር አቀፍ ደረጃ በዛሬው ዕለት የሚካሄደውን ሀገራዊ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር በወላይታ ሶዶ ከተማ ከሚገኙ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመሆን በማህበሩ የኮካቴ እንስሳት እርባታ ማዕከል ቅጥር ግቢ አካሂደዋል፡፡ በችግኝ ተከላ መርሀ ግብሩ የወላይታ ልማት ማህበር ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሰፋ ናና

በመትከል ማንሰራራት Read More »

ማህበሩ ከየትኛዉም ጊዜ ይልቅ የአባላት ድጋፍ እንደሚያስፈልገዉ ተነገረ።

በወላይታ ልማት የጠበላ ከተማ ቅርንጫፍ አባላት ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ በዛሬዉ ዕለት ተካሂዷል ።በጉባኤው የከተማዉ የልማት ማህበሩ አባላት የተገኙ ሲሆን የማህበሩና የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የ2024 እ.አ.አ ክንዉን ሪፖርትና የ2025 ዕቅድ በዝርዝር ቀርበዉ ዉይይት ተደርጎባቸዉ ጸድቀዋል።ጉባኤዉን በንግግር የከፈቱት የጠበላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ እጩ ዶ/ር ታረቀኝ ገቼረ ማህበሩ በአሁን ጊዜ ከማንኛውም ጊዜ ይልቅ የአባላት ድጋፍ ይሻል በማለት ማህበሩን ማጠናከር

ማህበሩ ከየትኛዉም ጊዜ ይልቅ የአባላት ድጋፍ እንደሚያስፈልገዉ ተነገረ። Read More »

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በአረካ ከተማ የሚገኝውን የወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤት ጎበኙ!።

በወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤት ጉብኝታቸው ተማሪዎች ትምህርታቸውን ጠንክረዉ እንዲማሩ ምክር ሰጥተዋል። ለትምህርት ቤቱ ውጤታማነት ሁሉም ባለ ድርሻ አካለት በቅንጅት መስራት እንደሚገባቸዉ አሳስበዎል በጉብኝቱ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጴጥሮስ ወ/ማርያምን ጨምሮ የዞኑና የአረካ ከተማ አመራሮች ተገኝተዋል።

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በአረካ ከተማ የሚገኝውን የወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤት ጎበኙ!። Read More »

ከጎዳና ለተመለሱ ልጆች ወላጆች የንግድ ስራ መነሻ ካፒታልና ንብረት ተሰጣቸው፡፡

ወላይታ ልማት ማህበር አሜሪካን ሀገር ኮሎራዶ ግዛት ዴንቨር ከተማና አካባቢው ከሚገኙ የወላይታ ተወላጆች ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ከተለያዩ አካባቢዎች ወደ ወላይታ ሶዶ ከተማ በመምጣት ኑሮአቸውን በጎዳና ላይ ያደረጉ ህጻናትን ወደቤተሰቦቻቸው በመመለስ ማቋቋሙ ይታወቃል፡፡ ማህበሩ እነዚህን ህጻናት በማቋቋምና በዘላቂነት የልጆቹን ቤተሰብ ኑሮ ለማሻሻል በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሆነ የሚታወስ ሲሆን ለልጆቹ የትምርት ቁሳቁስ፣ ቀለብ፣ የጤና መድህን ሽፋንና ሌሎች

ከጎዳና ለተመለሱ ልጆች ወላጆች የንግድ ስራ መነሻ ካፒታልና ንብረት ተሰጣቸው፡፡ Read More »

“ልማት ማህበሩ ለዞኑ ሁለንተናዊ ብልጽግና አስተዋጽኦ ያላቸው በርካታ አኩሪ ተግባራት አከናውኗል።”አቶ ጴጥሮስ ወልደማርያም

የወላይታ ልማት ማህበር (ወልማ) 24ኛ ዓመት መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን እያካሄደ ነው። ጉባኤውን በመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩት የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የማህበሩ የበላይ ጠባቂ አቶ ጴጥሮስ ወልደማርያም የወላይታ ልማት ማህበር ባለፉት 24 ዓመታት በግብርና በሥራ ዕድል ፈጠራ በጤና በንፁህ መጠጥ ውሃ እና በመሠረተ ልማት ሥራዎች ለዞኑ ሁለንተናዊ ዕድገት አስተዋጽኦ ያላቸው በርካታ ተግባራት ተፈጽመዋል ብለዋል። የህዝባችን ፍሬ የሆነው

“ልማት ማህበሩ ለዞኑ ሁለንተናዊ ብልጽግና አስተዋጽኦ ያላቸው በርካታ አኩሪ ተግባራት አከናውኗል።”አቶ ጴጥሮስ ወልደማርያም Read More »