የማህበሩ 25ኛ ዓመት የአባላት መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ እየተካሄደ ነዉ

የጉባኤውን መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግሥት ዋና ተጠሪ እና የወላይታ ልማት ማህበር ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ገብረመስቀል ጫላ እንደተናገሩት ወላይታ ማንነቱን ጠብቆ የኖረ፤ የዳበረና ተዝቆ የማያልቅ ባህል ያለው ህዝብ ነው። የወላይታ ህዝብ እንግዳ ተቀባይ፣ በመቻቻልና በመከባበር ከሌላው ጋር አብሮ የሚኖር ድንቅ እሴቶች ባለቤት ነው። የዘመኑ ትውልድ የአባቶችን ጠንካራ የሥራ ባህልን፣ ጀግንነትን፣ አብሮነትን […]

የማህበሩ 25ኛ ዓመት የአባላት መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ እየተካሄደ ነዉ Read More »

በእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በመስራት ግብርናን ለማዘመን የሚያስችል ውይይት ተደረገ፡፡

ወላይታ ልማት ማህበር በዞኑ በሚያከናውናቸው የልማት ስራዎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ ዘመናዊ አሰራሮችን በመተግበር የእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ለማድረግ ይሰራል፡፡ ማህበሩ ባሳለፍነው ዓመት ከወላይታ ዞን አስተዳደርና ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመሆን ይህንን የቴክኖሎጂ ሽግግር ስራን ለማሳደግ የስራ መሪዎች በሀገረ አየርላንድ ልምድ እንዲቀስሙ ማድረጉ የሚታወስ ነው፡፡ በዚህም ወቅት የስራ መሪዎቹ የተለያዩ ኩባንያዎችን የጎበኙ ሲሆን የትራክተር ማምረቻ ፋብሪካ ተጠቃሽ

በእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በመስራት ግብርናን ለማዘመን የሚያስችል ውይይት ተደረገ፡፡ Read More »

ተቋማትን በማጠናከርና በማስቀጠል ረገድ ሁሉም ሰራተኞች ድርሻ እንዳላቸው ተገለጸ፡፡

ወላይታ ልማት ማህበር ላለፉት 25 ዓመታት በሰራተኞች ቁርጠኝነትና በጠንካራ አመራር በህዝቡ ውስጥ ገብቶ በመስራት ሰፊና ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራትን እያከናወነ እንደቆየ ይታወቃል፡፡ ማህበሩ እነዚህን ተግባራት ለማስፋፋትና ይበልጥ ህዝቡን ተጠቃሚ ለማድረግ የተለያዩ የሪፎርም ስራዎችን እየሰራ ቆይቶ የበላይ አመራር ለውጥ በማድረግ ወደ ስራ ገብቷል፡፡ በዛሬው ዕለት አዲስ የተመደቡ አመራሮች ከወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤቶች ሰራተኞች

ተቋማትን በማጠናከርና በማስቀጠል ረገድ ሁሉም ሰራተኞች ድርሻ እንዳላቸው ተገለጸ፡፡ Read More »

የወላይታ ልማት ማህበር በሦስት መቶ ሚሊየን ብር ወጪ የትራክተር ፣ባክሎቤር እና ግሬደር ግዢ ፈፀመ።

‎ማህበሩ ከሞኤንኮ ኢትዮጵያ የገዛቸውን ትራክተሮች እና ለመንገድ ሥራ አገልግሎት የሚውሉ ማሽኖችን በዛሬው ዕለት በወላይታ ጉተራ ሆቴል፣ ቱሪዝምና ስልጠና ማዕከል ላይ በመገኘት ተረክቧል ። ‎ማህበሩ ከምስረታው አንስቶ በዘላቂ ኑሮ ማሻሻል ላይ ትኩረቱን በማድረግ በርካቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉ አይዘነጋም ። በግብርናው ዘርፍ ከአርሶ አደሩ ጎን በመሆን ከመስራት ባለፈ ግብርናን በማዘመን ኋላ ቀር አሰራሮችን በመተው ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም

የወላይታ ልማት ማህበር በሦስት መቶ ሚሊየን ብር ወጪ የትራክተር ፣ባክሎቤር እና ግሬደር ግዢ ፈፀመ። Read More »

የኢትዮ- ቻይና ወዳጅነትና ትብብር ኮሚቴ ከወላይታ ልማት ማህበር ጋር በጋራ ለመሰራት የሚያስችል ስምምነትን ተፈራረሙ።

የኢትዮ- ቻይና የወዳጅነት ትብብር ኮሚቴ ከወላይታ ልማት ማህበር ጋር በተለያዩ ስራዎችን በጋራ ለመሰራት ተፈራርሟል። የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪና የልማት ማህበሩ የበላይ ጠበቃ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ ኢትዮጵያና ቻይና ለረጅም ዘመናት የቆየ ግንኙነት ያላቸው ሀገር መሆናቸውን ገልፀዋል። ወላይታ ምቹ የአየር፣ የውሃ አማራጮች፣ ሰፋፊ የለም መሬቶች እና የተማሩ ዜጎች የሚኖሩበት አከባቢ መሆኑንም ገልጸዋል። የኢትዮ- ቻይና ወዳጅነትና ትብብር

የኢትዮ- ቻይና ወዳጅነትና ትብብር ኮሚቴ ከወላይታ ልማት ማህበር ጋር በጋራ ለመሰራት የሚያስችል ስምምነትን ተፈራረሙ። Read More »

ለተማሪዎች የሚቀርበው ወተት ጥራቱና ደህንነቱ የተጠበቀ መሆን እንደሚገባው ተገለጸ፡፡

ወላይታ ልማት ማህበር በወላይታ ዞንና በወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር SNV ከተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር የወተት ምርትና ምርታማትን ለማሳደግ BRIDGE+ ፕሮጀክት እየተገበረ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ከፕሮጀክቱ ተግባራት አንዱ የትምህርት ቤቶች ወተት ምገባ ሲሆን በዚህም ተማሪዎች በስነ ምግብ ዳብረው ትምህርትን በአግባቡ ተከታትለው መፃኢ ተስፋቸው ብሩህ እንዲሆን በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡ማህበሩ ለሚተገብረው የትምህርት ቤት ወተት ምገባ ተግባር የሚውለውን የወተት

ለተማሪዎች የሚቀርበው ወተት ጥራቱና ደህንነቱ የተጠበቀ መሆን እንደሚገባው ተገለጸ፡፡ Read More »

ለልጆች አካላዊ እና አዕምሮአዊ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው የተማሪዎች የወተት ምገባ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለፀ ።

‎ይህ የወተት ምገባው ፕሮግራም በወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር እና በወላይታ ልማት ማህበር SNV BRIDGE+ ፕሮጀክት ትብብር በከተማው ባሉ 8 የመንግስት ቅድመ መደበኛ ት/ቤቶች ላይ እየተተገበረ የሚገኝ ሲሆን አጠናክሮ ለማስቀጠል በማሰብ ከማህበሩ ማኔጅመንት አባላት እና ከተወጣጡ ከማህበሩ ሠራተኞች ጋር ውይይት ተደርጓል ። ‎በመድረኩ የተገኙት የወላይታ ልማት ማህበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሰፋ ናና በንግግራቸው ማህበሩ ይህን

ለልጆች አካላዊ እና አዕምሮአዊ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው የተማሪዎች የወተት ምገባ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለፀ ። Read More »

ወላይታ ልማት ማህበር የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማሳደግ የያዘውን ዕቅድ ዕውን ለማድረግ ከተለያዩ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ጋር እየሰራ ይገኛል ።

‎ማህበሩ በዛሬው ዕለትም ከዚህ ቀደም አብሮት ከሚሰራው ET-LEARNS ከተሰኘው ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመሆን ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 310 ክሮም ኮምፒውተር እና 10 ሰርቨሮችን ከነአክሰሰሪያቸው ለተለያዩ ት/ቤቶች አበርክቷል ። ‎‎በመድረኩ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የወላይታ ልማት ማህበር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ገብረመስቀል ጫላ የወላይታ ማህበረሰብ ያለውን

ወላይታ ልማት ማህበር የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማሳደግ የያዘውን ዕቅድ ዕውን ለማድረግ ከተለያዩ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች ጋር እየሰራ ይገኛል ። Read More »

‎ማህበሩ በተፈጥሮ አደጋ የተጎዱ ዜጎችን መልሶ በማቋቋም ረገድ የድርሻዉን እያበረከተ ነዉ።

‎ወላይታ ልማት ማህበር ዜጎች የተሻለ ኑሮ እንዲኖሩ ለማስቻል በያዘዉ ዕቅድ የተለያዩ ድጋፎችን በማመቻቸት የድርሻዉን እየተወጣ መቆየቱ ይታወቃል። ‎ማህበሩ ባሳለፍነዉ ዓመት በካዎ ኮይሻ ወረዳ በመሬት መንሸራተት አደጋ የተጎዱ ዜጎችን በመደገፍና መልሶ በማቋቋም ሂደት ከመንግስትና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር በመሆን የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ የቆየ ሲሆን በዛሬዉ ዕለት በዞነነ አስተዳደርና በተለያዩ አካላት ድጋፍ የሰራቸዉን መኖሪያ ቤቶች በአደጋዉ ምክንያት

‎ማህበሩ በተፈጥሮ አደጋ የተጎዱ ዜጎችን መልሶ በማቋቋም ረገድ የድርሻዉን እያበረከተ ነዉ። Read More »

ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚተገበር የትምህርት ፕሮጀክት ማስጀመሪያ ተካሄደ፡፡

ወላይታ ልማት ማህበር በሰው ሀብት ልማት ዘርፍ ከአጋር ድግርጅቶች ጋር በመተባበር በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረገ እንደቆየ ይታወቃል፡፡ ማህበሩ ከነዚህ አጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ከመንግስት ጎን በመሆን የራሱን ድርሻ አበርክቷል፤ እያበረከተም ነው፡፡ ማህበሩ በዛሬው ዕለት በወላይታ ዞን አምስት መዋቅሮች የሚተገብረውን የዳግም ትምህርት ዕድል ፕሮጀክት አስጀምሯል፡፡ ፕሮጀክቱ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልልና ከወላይታ ዞን ከተለያዩ

ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚተገበር የትምህርት ፕሮጀክት ማስጀመሪያ ተካሄደ፡፡ Read More »