News

WODA News

ማህበሩ ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ የኮምፒውተርና ሰርቨር ድጋፍ አገኘ፡፡

ወላይታ ልማት ማህበር የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን ለማሳደግ ከተለያዩ አጋር ድርጅቶች ጋር በትብብር እንደሚሰራ ይታወቃል፡፡ ማህበሩ በትብብር ከሚሰራቸው ተቋማት አንዱ የሆነውና ከዚህ በፊት ከማህበሩ ጋር በመሆን በዞኑ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ትምህርትን ለማስፋፋት የራሱን ድርሻ እያበበረከተ የቆየ ET-LEARNS የተሰኘው ግብረ ሰናይ ድርጅት ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገዙ ኮምፒውተሮችና ሰርቨር ለልማት ማህበሩ አበርክቷል፡፡ ድጋፉ 310 ክሮም ቡክ […]

ማህበሩ ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ የኮምፒውተርና ሰርቨር ድጋፍ አገኘ፡፡ Read More »

ማህበሩ ከGIZ ሰባት ሚሊዮን ብር የሚጠጋ የእርሻ መሳሪያዎች ድጋፍ ተደረገለት፡፡

ወላይታ ልማት ማህበር በዘላቂነት የማህበረሰቡን ኑሮ ለማሻሻል በያዘው ዕቀድ በዞኑ ውስጥ ያሉ አርሶ አደሮች ዘመናዊ የግብርና አስተራረስ እንዲለማመዱ ከተለያዩ ግብረሰናይ ደርጅቶች ጋር በመተባበር ይሰራል፡፡ ማህበሩ የመስኖ እርሻንና የንብ ማነብ ስራን ለማዘመን፣ የወተት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ወዘተ… ስራዎችን በመስራት አያለ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እንዳደረገና እያደረገ እንደቆየ ይታወቃል፡፡ ልማት ማህበሩ በዚሁ ዘርፍ በሚያደርገው ርብርብ GIZ የተሰኘ የጀርመን

ማህበሩ ከGIZ ሰባት ሚሊዮን ብር የሚጠጋ የእርሻ መሳሪያዎች ድጋፍ ተደረገለት፡፡ Read More »

የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ወላይታ ሊቃ ትምሀርት ቤትን ጎበኙ።

በተለያዩ አካባቢዎች የልማት ስራዎችን እየጎበኘ ያለዉና በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራዉ ልዑካን ቡድን በወላይታ ሶዶ ከተማ ተገኝተዉ የተሞክሮ ማዕከል የሆነዉን ወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤትን ጎብኝቷል። ልዑካን ቡድኑ በትምህርት ቤቱ ያለዉን የመማር ማስተማርና ሌሎች ተግባራትን በወላይታ ልማት ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሰፋ ናና ማብራሪያ ተሰጥቶታል ። ዶ/ር መቅደስ በጉብኝቱ የትምህርት ቤቱን ተማሪዎች በክፍሎች፣

የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ወላይታ ሊቃ ትምሀርት ቤትን ጎበኙ። Read More »

በዛሬው ዕለት የወላይታ ሊቀ ትምህርት ቤት ፍሬ የሆኑ 31 የህክምና ዶክተሮች ከሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተመርቀዋል፡፡

ወላይታ ልማት ማህበር ከድህነትና ኋላ ቀሪነት የተላቀቀ ወላይታን የማዬት ራዕዩን እውን ለማድረግ ትምህርት ወሳኝ መሳሪያ መሆኑን በማመን በኢትዮጵያ ሚሊኒዬም ወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤትን አቋቋመ፡፡ ትምህርት ቤቱ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ በስኬት ጎዳና በመጓዝ ከሀገር ውስጥ አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ተማሪዎችን በማፍራት አካባቢውን በበጎ ጎን ስሙ ከፍ እንዲል የራሱን ሚና ሲጫወት ቆይቷል፡፡ ትምህርት ቤቱ ከ2005 ዓ.ም

በዛሬው ዕለት የወላይታ ሊቀ ትምህርት ቤት ፍሬ የሆኑ 31 የህክምና ዶክተሮች ከሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተመርቀዋል፡፡ Read More »

ማህበሩ በወላይታ ሊቃ ት/ቤት ባለአንድ ብሎክ የመማሪያ ህንጻ ግንባታ አስጀመረ፡፡

ወላይታ ልማት ማህበር በሀገር አንዲሁም በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ስመጥር እና ተወዳዳሪ ተማሪዎችን በማፋራት የሚታወቀውን ወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤትን ለማጠናከርና ለማስፋፋት በያዘው ዕቅድ ባሳለፍነው ዓመት የሀብት ማሰባበሰቢያ መርሀ ግብር በመንደፍ የተለያዩ አካላትን በማሳተፍ ሀብት ማሰባበሰቡ ይተወቃል፡፡ ለትምህርት ቤቱ ማስፋፊያና ማጠናከሪያ ድጋፍ ለማድረግ በወቅቱ ቃል ከገቡ ባለሀብቶች መካከል ሀጂ ሙስጠፋ አወል (የሙለጌ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ባለቤት) እና ቤተሰቡ አንዱ

ማህበሩ በወላይታ ሊቃ ት/ቤት ባለአንድ ብሎክ የመማሪያ ህንጻ ግንባታ አስጀመረ፡፡ Read More »

በ9 ወራት ከ98 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ ሀብት በመሰብሰብ በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡

ወላይታ ልማት ማህበር ከድህነትና ኋላቀርነት የተላቀቀ ወላይታን የማየት ትልሙን ለማሳካት በዞኑ ሁሉም አካባቢዎች የልማት ተግባራትን እያከናወነ ነው፡፡ ማህበሩ በ2024 እ.አ.አ በሰው ሀብት ልማት፣ በዘላቂ የኑሮ ማሻሻያና በተቀናጀ ጤና ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ አቅዶ በመነሳት ላለፉት 9 ወራት የልማት ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቶ አፈጻጸሙን ገምግሟል፡፡ በግምገማው ማህበሩ በዓመቱ በ9 ወራት ከ98 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ ሀብት በመሰብሰብ የልማት

በ9 ወራት ከ98 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ ሀብት በመሰብሰብ በርካታ ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡ Read More »

ማህበሩ የወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤት ጥንካሬውን እንደሚያስቀጥል ተነገረ፡፡

በወላይታ ልማት ማህበር የሚተዳደረው የወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤት በወላይታ ሶዶ ከተማ ብቻ ሀኖ በአገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ደረጃ ስመ ጥር ሆኖ ውጤታማ ተማሪዎችን እያፈራ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ ማህበሩ በያዝነው 2017 የትምህርት ዘመን የትምህርት ቤቱን ቁጥር በመጨመር በዞኑ ሶስት አካባቢዎች በይፋ ስራ አስጀምሯል፡፡ በዛሬው ዕለት አራተኛው የወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤት በገሱባ ከተማ አስተዳደር በይፋ ስራ ጀምሯል፡፡

ማህበሩ የወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤት ጥንካሬውን እንደሚያስቀጥል ተነገረ፡፡ Read More »

ማህበሩ በዞኑ ሶስተኛውን የወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤት ስራ አስጀምሯል።

የወላይታ ልማት ማህበር ላለፉት ጊዜያት በወላይታ ዞን በቁጥር አንድ ብቻ የነበረውን የወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤት ለማስፋፋት በያዘው ዕቅድ በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ሶስት ትምህርት ቤቶችን ለመከፈት እንቅስቃሴ ጀምሮ ዕቅዱን በማሳካት በያዝነው ሳምንት ሁለተኛውን ትምህርት ቤት በአረካ ከተማ አስተዳደር በይፋ ስራ ማስጀመሩ ይታወሳል፡፡ በዛሬው ዕለት ደግሞ በቦዲቲ ከተማ አስተዳደር በዞኑ ሶስተኛውን የወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤት በይፋ

ማህበሩ በዞኑ ሶስተኛውን የወላይታ ሊቃ ትምህርት ቤት ስራ አስጀምሯል። Read More »

በዛሬዉ ዕለት የወላይታ ሊቃ አረካ ትምህርት ቤት በይፋ ስራ ጀምሯል።

በማስጀመሪያዉ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጴጥሮስ ወልደማርያምን ጨምሮ ሌሎች የወላይታ ዞን የስራ ኃላፊዎች፣ የወላይታ ልማት ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሰፋ ናና እና የወልማ ማኔጅመንት አባላት ተገኝተዋል። በቀጣይ ቀናትም የቦዲቲና ገሱባ ትምህርት ቤቶች በይፋ ተከፍተዉ ስራ የሚጀምሩ ይሆናል።

በዛሬዉ ዕለት የወላይታ ሊቃ አረካ ትምህርት ቤት በይፋ ስራ ጀምሯል። Read More »

ወላይታ ልማት ማህበር የሚያስተዳድራቸው የሊቃ ትምህርት ቤቶች ቁጥር ወደ አራት ከፍ አለ፡፡

ወላይታ ልማት ማህበር ላለፉት 16 ዓመታት በዞኑ ማዕከል ወላይታ ሶዶ አንድ ትምህርት ቤት ከፍቶ ብሩህ አዕምሮ እያላቸው በኢኮኖሚ አቅም ማነስ ምክንያት ጥራት ያለውን ትምህርት ማግኘት ያልቻሉ ተማሪዎችን ሙሉ ስኮላርሺፕ በመስጠትና ወጪ የሚጋሩ ተማሪዎችን በመቀበል ጥራት ያለውን ትምህርት በመስጠት ከወላይታ ዞን አልፎ በደቡብ ክልልና በሀገር አቀፍ ደረጃ በርካታ የህክምና ዶክተሮችን፣ መሀንዲሶችንና በሌሎች ሙያ የተሰማሩ ባለሙያዎችን አፍርቷል፤

ወላይታ ልማት ማህበር የሚያስተዳድራቸው የሊቃ ትምህርት ቤቶች ቁጥር ወደ አራት ከፍ አለ፡፡ Read More »