ልማት ማህበሩ ከሳቫና ፕሪንቲንግ ጋር በመተባበር ለአራት ትምህርት ቤቶች ከ1.1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አበረከተ።

የዘንድሮ ድጋፍ የተደረገዉ በአረካ፣ ወላይታ ሶዶና ቦዲቲ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም ዳሞት ጋሌ ወረዳ ሲሆን በነዚህ መዋቅሮች በሚገኙ አራት ትምህርት ቤቶች ላሉ ቅድመ መደበኛና አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ነዉ።